Thursday, August 29, 2013

ሰላም ለሁላችሁ፤- ቅ/ጴጥሮስ በደብረታቦር የጌታውን ብርሃን ሲመለከት ድፍት ብሎ ወደቀ፣ማቴ 17;6 ቅ/ዮሐንስ በራዕይ ጌታ ኢየሱስን በሰባቱ መቅረዞች መሃል ሲመለከተው እንደሞተ ሰው ሆኖ ወደቀ፡



ሰላም ለሁላችሁ፤- ቅ/ጴጥሮስ በደብረታቦር የጌታውን ብርሃን ሲመለከት ድፍት ብሎ ወደቀ፣ማቴ 17;6 ቅ/ዮሐንስ በራዕይ ጌታ ኢየሱስን በሰባቱ መቅረዞች መሃል ሲመለከተው እንደሞተ ሰው ሆኖ ወደቀ፡፡ራዕ 1;17 ሁለቱም ግን ተመልሰው ተነስተው የእግዚአብሔርን ሀሳብ  አገልግለዋል፡፡ በእግዚአብሔር ፊት መሆን እየወደቁ እየተነሱ ነው፡፡ልጅ በአባቱ ፊት የሚያድገው እየወደቀ እየተነሳ ነውና፡፡ ማንም ሰው በጌታው ፊት እንኳ ሆኖ በራሱ ጸንቶ አይቆምም፡፡ የራሱ ጉልበት፣የራሱ ጽድቅ፣ ማስተዋሉ ይከዳዋል፡፡ ነገር ግን ከፊቱ የቆመው አባት እንደ ቅ/ጴጥሮስ እጁን ዘርግቶ ከመስጠም ያድነዋል እንጂ! እንደገና ያቆመዋል እንጂ! ስለዚህ በፊቱም ሆኜ ራሴን ማስተካከል ስላልቻልኩ ወደ ዓለሜ ብመለስ ይሻላል ብላችሁ የሞኝ ውሳኔ እንዳትወስኑ፡፡ ጌታችሁ ራሱን ያስተካከለውን አልጠራም ይልቁንም እናንተ ደካሞች ሸክም የከበደባችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ አለን እንጂ፡፡ ማቴ 11፤28
 እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment