Friday, January 10, 2014



ሰላም ለሁላችሁ፤- አንድ የህክምና ዶክተር በባህር ዳርቻ ንፋስ ሲቀበል ባህሩ ላይ የሚዋኙ ዳክዬዎች ትንሽ እንደዋኙ ፍግም ብለው እንደሚሞቱ ተመለከተ፡፡ ሁኔታውን ሲያጠና የዳክዬ በሽታ እንደያዛቸው ተረዳ፡፡ ሄዶም በቤተ ሙከራ ለወፎቹ መድሃኒት ፈለሰፈ፡  መድሃኒቱን ይዞ መጥቶ ሊሰጣቸው ሲሞክር ዳክዬዎቹ ሊቀርቡት አልቻሉም፡፡ ሲጠራቸው እየፈሩ ይሸሹ እና ይሞቱ ነበር፡፡ አይኑ እያየ ዳክዬዎቹ አለቁ፡፡ ዶክተሩም እነዚህ ዳክዬዎች ወደ እኔ መቅረብ የፈሩት አኔ አነሱን ስላልመሰልኩ ነው እኔ ዳክዬ ብሆን ኖሮ ቀርቤ አክማቸው ነበር አለ፡፡ አምላክ ለምን ሰው ሆነ ትላላችሁ? የሚሉ ሰው መሆኑም ክበሩን እንደማይመጥን የሚገምቱ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ነገር ግን አምነንበት አንድንድን በመድሃኒቱም፣ እንድንፈወስ፣እኛነታችንን የሚረዳ ጌታ በሥጋ ተገልጧል፡፡ሰው መሆኑን የትትናውን እና የፍቅሩን ውሳኔ ማመን ያጸድቃል፡፡ ጥንት በሙሴ ዘመን በሲና ተራራ በእሳት ተገልጦ ድምጹን ልንሰማ አንችልም እንሞታለን ብለን ፈርተን ሸሽተን ነበር፡፡ዛሬ ግን እኛን መስሎ በሥጋ ስለተዛመድን የልባችን አምላክ እና እውነተኛ አባት አድርገነዋል፡፡
እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት