Tuesday, August 6, 2013



ሰላም ለሁላችሁ፤- ይህ የእመቤታችን መታሰቢያ ጾም ሁላችንም በፍቅር የምንጾመው ብዙ በረከትም የተቀበልንበት ነው፡፡ ማርያም ድንግል ጌታችንን ለመውለድ ፍቃደኛ በመሆኗ እና ከእርሱም ጋር እስከ ስቅለቱ አሳዛኝ የመከራ ጊዜ በማሳለፏ በስሟም በተቀበልነው ድንቅ በረከት ከልባችን እንወዳታለን፡፡ ቅድስት ሆይ ለምኝልን ብለን በምንጸልየው ጸሎት ብዙ መልስ እንዳገኘን ሁሉ በእነዚህም ሳምንታት በጸሎቷ እና እምነታችንን በሚያውቀው ልጇ ዘንድ እንደምንሰማ አንጠራጠርም፡፡ውሃው ወይን እንዲሆን ጋኖቹ መታጠብ ነበረባቸው፡፡ እኛም እንዲሁ ነን፡ ይህን ጽሁፍ የምታነቡ ሁሉ ወደ ንስሃ አባት ሄደን ተናዘን በጌታም ፊት በተሰበረ መንፈስ ልንቆም፣ ሥጋውን ልንበላ ደሙን ልንጠጣ ይገባል፡፡ የጸሎት ርዕስ ይዘን ልንጾም ይገባናል፡፡ በዓለም ላይ ስላሉ እርዳታ ስለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ልንጸልይ ይገባል፡፡ በሶርያ ብዙ ክርስቲያኖች ሌሎችም ወንድሞች በጦርነት እየተፈጁ ነው፡፡ በግብጽም ክርስቶሳውያን አደጋ ላይ ናቸው፡፡ ለምንወዳት ሃገራችንም፣ ለወንጌል መስፋፋት፣ ርኩሰት የተሞላችውን ይህችን ዓለም ለተቀላቀሉ ሕጻናት ከጥፋት እንዲድኑ፣ አባቶቻችን ፍርድ ጽድቅ እንዳይለያቸው፣ መሪዎቻችን ህዝባቸውን እና ሃገራቸውን እንዲወዱ፣ መንፈስ ቅዱስ በልባችን እንዲሰራ ከልባችን ልንጸልይ ይገባል፡፡….የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ ታላቅ ሃይል ታደርጋለችና፡፡ያቆ 5:16 ቅድስት ሆይ ለምኝልን
እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment