Tuesday, July 8, 2014

ሰላም ለሁላችሁ፤- አገልግሎት ፍላጎት ነው ወይስ ቅባት?

ሰላም ለሁላችሁ፤- አገልግሎት ፍላጎት ነው ወይስ ቅባት? ዛሬ ብዙ ሰው መናገር ስለሚቻል ሰባኪ እንደሚኮን ትንሽ የማይሻክር ድምጽ ካለ መዘመር እንደሚቻል የሚያስቡበት ጊዜ ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ አርቲስቱና ዘፋኙ በትርፍ ሰዓቱ ዘማሪ ነው፡፡ በክብረ በዓላት ቀን ደግሞ ቅልጥ ያለ ጨፋሪ ሆኖ ይቆማል፡፡ በትርፍ ሰዓትሽ ምን ያደስትሻል ተብላ አንዲት አርቲስት በቀደም እሁድ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ተጠየቀች፡፡ ለስለስ ያለሙዚቃ በተለይ የሚያስጨፍር ከሆነ ምድር አይበቃኝም አለች፡፡ ይህችው ሴት ለቤተክርስቲያን መርጂያ መዝሙር ዘምራ/ ለቤተክርስቲያ ያረገችውን መልካም ስራ ባደንቅም/ በየቤተክርስቲያኑ መድረክ አትጠፋም፡፡ አንዳንዴም ቤተክርስቲያን ተደፈረች ድረሱ የሚል ሃሳብ ወለድ ድራማዎችን እየሰሩ የእነሱ መቅደስ /ሰውነታቸው/ ዓለምን የሚያገለግልና ውሳኔአቸውም ለእግዚአብሔር ያልተሰጠ ሆኖ ይታያል፡፡ አንዱ አርቲስት ቀደም ብሎ ጥሩ የሚባል ዝማሬ ሰራ፡፡ ቆየት ብሎ በአንድ መጽሔት እኔ ዘማሪ መሆን አልፈልግም ቤተክርስቲያንን ለመርዳት ነው! ብሎ ቃለምልልስ ሰጠ፡፡ እግዚአብሔር ጉሮሮ ሳይሆን ልብ ነበር የሚያስፈልው፡፡ የሚቃጠል መስዋት ደስ አያሰኝህም የእግዚአብሔር መስዋት የተሰበረ ልብ ነው፡፡ መዝ50፡17 አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት የተቀቡ ለዚህ አገልግሎት ራሳቸውን የሰጡትን ዘማሪያንን አይናችሁ ላፈር ብለው እኒሁ የሁለት ቤት ሰዎችን ልዩ አገልጋያቸው አድርገው ይሰይማሉ፡፡ ማንም ሰው ለጌታው ክብር ሊሰጥ እንደሚገባ አምናለሁ፡፡ ነገር ግን አውደ ምህረቱና መቅደሱ እግዚአብሔር በጸጋው ቅባት በለያቸው ሰዎች ነው መገልገል ያለበት፡፡ የእግዚአብሔር የሆነ ልዩ ነገር ከሌለ ቅድስና እንዴት ይለያል? የተነሳ ሁሉ ነፍሱን ለጌታው ብቻ ወስኖ ሳይሰጥ ላገልግል ካለ ዓለማዊነት ሰተት ብሎ ወደ ቤተክርስቲያን ይገባል፡፡ቤተክርስቲያ የምትጠፋበት ዋናው መንገድ ዓለማዊነት መንፈሳዊ ለምድ ለብሶ ሲገባባት ነው፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ዘፋኞች በድምጻቸው ብቻ ዘማሪዎች ነበሩና ትንሽ ከፍ ሲሉ የተደቁ ዘፋኞች ወደ መሆን ይቀየራሉ፡፡ እድገቱ ከዘማሪነተት ወደ ዘፋኝነት የሆነ ይመስል ያኔ የሰንበት ተማሪ ዲያቆን ነበርኩ ይሉናል፡፡ ማንም ይህን ሆኖ ከሆነ ዘፋኝ የሆነው እንዲህ ብሎ በመናገሩ ማፈር አለበት፡፡ እግዚአብሔር በቂ እንጀራ ነው፡፡ እግዚአብሔር ትልቅ ጥበብ ነው፡፡ እርሱ የዚህ ዓለም ጥበብ የማይደግፈው ራሱን የቻለ ብልጥግና ነው፡፡ሰው ወደ እግዚአብሔር የሚመጣው ጌታን ሊያግዝ ሳይሆን ራሱን ሰው አድርጎ ሊሰራ ነው፡፡ ፈርቶ፣ ትሁት ሆኖ፣ ለመናገር ሳይቸኩል ደግሞም በእምነት አድጎ ዓለሙን ርግፍ አድርጎ ሊኖር መሆን አለበት፡፡ አገልግሎትም በቅባት እና በመጠራት እንጂ በታለንት ወይ በችሎታ አይደለም፡፡ በመንፈሴ እንጂ በሐይልና በብርታት አይደለም ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፡፡ ዘካ 4፤6 ከእናንተ ብዙዎች አስተማሪዎች አይሁኑ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና፡፡ ያዕ 3፤1 እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት