Friday, August 23, 2013



ሰላም ለሁላችሁ፤- ሙሴ በቤቱ ሁሉ እንደ ሎሌ የታመነ ነበረ፡፡ ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ላይ ታመነ ነው፡፡ዕብ 3፤5 እግዚአብሔርን እንደ ባርያ ከህጉና ከቅጣቱ ተነስቶ መፍራት አንድ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን እንደ ልጅ ከምህረቱ እና ከተወደደ አባትነቱ ተነስቶ መፍራት ግን እጅግ የተሻለ ነው፡፡ ምክንያቱም ህጉ ፍጹም ካልሆኑ አይምርም፡፡ ህጉ አሰሪ ነው ያልሰራውን አይከፍለውም ይከሰዋል እንጂ፡፡ ከዚህ የተነሳ ሰው በደከመ ጊዜ ተስፋ ቆርጦ ከእግዚአብሔር ፊት እንደቃየል ሊኮበልል ይችላል፡፡ ትህትናውም ፍርሃቱም ቅጣትን ብቻ ፈርቶ ይሆንና በአምላኩ መኖር አሰልቺ ሥራ ይሆንበታል፡፡ምህረቱን ያመነ ግን ሁል ጊዜ በፍቅሩ ይደገፋል፡፡ ምህረቱ ለዘለዓለም ነውና በዚህ እምነት ውስጥ ተስፋ መቁረጥ የለም፡፡ መዝ 135፤1 እንደ ልጅም በቤቱ /በቤተክርስቲያን/ የሚኖር የአባቱን ቤት እንደራሱ ቤት ይመለከታል፡፡ስለቤቱ ሥነስርዓት አስተማሪ አይፈልግም፡፡ ስለ ቤተሰቦቹም ክብር ሌላ ባዕድ አስረጂ አይፈልግም፡፡ ስለወላጆቹ አጠራር እና ቁልምጫ ፍቅሩ እንጂ በር ላይ የሚለጠፍ ማሳሰቢያ አያስረዳውም፡፡እንደ ልጅ አምኖ መኖር የአማኙን ነፍስ ሰላማዊ ያደርጋታል፡፡ ያደላድላታል፡፡
 እባክዎ ለሌሎች      ሼር ያድርጉት

No comments:

Post a Comment