Saturday, September 7, 2013

አይናማ ፍቅር_ ክፍል አንድ/በቀሲስ አሸናፊ/ ይሄ ፍቅር ስሜትን ኮርኳሪ ሆኖ በሃይል ሊጀምር ይችላል አንዳንዴ ይከሰታል ሳይባል በመላመድ ሊጀምር ይችላል፡፡፡፡

አይናማ ፍቅር_ ክፍል አንድ/በቀሲስ አሸናፊ/
ይሄ ፍቅር ስሜትን ኮርኳሪ ሆኖ በሃይል ሊጀምር ይችላል አንዳንዴ ይከሰታል ሳይባል በመላመድ ሊጀምር ይችላል፡፡፡፡ ንጥቅ የሚያደርግ፣ ደስታ የሚፈጥር፣ በተለይ ለልብ እረፍት የሚሰጥ ሆኖ ይሰማል፡፡ይህ ፍቅር ብዙ ጊዜ በጊዜው ይጀምራል፡፡ ሰውየው ራሱን ለኑሮ ባዘጋጀ ጊዜ ተረጋግቶ ይከሰታል፡፡ ሲግልም እንደሸክላ ምጣድ ነው፡፡ ቀስ ብሎ ይጀምራል እየቆየ ሲመጣ እየሞቀ ይመጣል፡፡ መብረጃ የሚባልጊዜ ገደብ የለውም፡፡ አብርሃምና ሣራ በዚህ ፍቅር ውስጥ ነበሩ፡፡ ካረጁ ከሸመገሉ በኋላ ተቃቅፈው ይተኙ ነበረ፡፡ ልጅንም የወለዱትም በዚሁ ፍቅር ውስጥ ካረጁ በኋላ ነበር፡፡ ይሄ ፍቅር ከውጫዊው ደም ግባት ብቻ አይነሳም ውስጥን በጥልቀት የማየት ድፍረት አለው፡፡ የሚያየውም ቀምሶ ለመትፋት አይደለም፡፡ ያፈቀረውን የሚሸከምበት መላ ለማበጀት ነው እንጂ! በእርሱ ዘንድ መልክ ደም ግባት ቦታ የላቸውም እያልኩ አይደለም ዋናው መለኪያው ግን የውስጥ ማራኪነት ነው፡፡ በዚህ ፍቅር የተያዙ ሰዎች የሚደንቅ ስብዕና አላቸው፡፡ ሁሌ ይፍለቀለቃሉ፡፡ ወቀሳ ማብዛትና በራስ የመተማመን ችግር የለባቸውም፡፡ ፍቅረኛቸው የትም ብትሄድ የትም ቢሰራ ቅናት የተባለ ስሜት አይሰማቸውም፡፡ ይልቁንም ለሩቁ ሰዋቸው መልካም እየለመኑ ይታገሳሉ እንጂ፡፡ ሐዋርያው ፍቅር አይቀናም እንዳለ፡፡1 ቆሮ 13;4
የአይናማው ፍቅር ሌላው ጠባይ ሁኔታዎች አይቀያይሩትም፡፡ ሣራ ከአብርሃም ጋራ በረሃቡ ዘመን ወደ ጌራራ ንጉስ በተሰደዱና ንጉሱ ሊያገባት በተዘጋጀ ጊዜ ንጉስ አግብታ ንግስት ከመሆን ከድሃው ባሏ ከአብርሃም ጋር ድህነትን መረጠች፡፡ዘፍ12;19 ፍቅሩ በዘመን፣ በሁኔታዎች፣ የተፈተነና ያለፈ ነው፡፡ በደህናም ጊዜ አፍቃሪ በችግርም ጊዜ አፍቃሪ፣ በረሃብም ዘመን በጥጋብ ጊዜ አፍቃሪ፣ ልጅ ሳይወልዱም አፍቃሪ ልጅ ወልዶም፣ ከስታም ጠቁራም አፍቃሪ ከስሮም ተጎሳቁሎም አፍቃሪ ነው፡፡ይህ ፍቅር እንደ አዋሽ ውሃ ቀስ እያለ ይሞላል፡፡ ሲፈስ ድምጹ አይሰማም/ጭቅጭቅ አይሰማበትም/ በጥልቀት ረዥም ርቀት ይሄዳል፡፡ ለውሳኔ አይቸኩልም ለመለያየትም ለመጋባትም ግራ ቀኙን ያያል፡፡በዚህ ፍቅር የተያዙ ሰዎች እንጀራም ይበላላቸዋል እንቅልፍም ይተኛላቸዋል፡፡ ፍቅሩ ጤነኛ በመሆኑ ጉዳት የሚባለውን ፉርጎ አያስከትልም፡፡ጸሎታቸውም ጌታ ሆይ ፍቃድህ ከሆነ ይሁን ካልሆነም ያንተ ፍቃድ ይሁን የሚል ነው፡፡ ካንቺ ከተለየሁ ሞት እመርጣለሁ ያላንተ መኖር አልችልም የሚሉ የሞኝ መዝሙሮችን አይዘምርም፡፡ እግዚአብሄር ያለእርሷ መኖር አለብህ ካለው ሳያጉረመርም ፍቃዱን ይቀበላል፡፡ እርሷም እንዲሁ! …..ይቆየን!
ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment