Tuesday, September 30, 2014

እንዲሁ መውደድ….. እንዴት የተወደዳችሁ ሆይ አንድ ሰው ጌታውን የሚወደው ለምንድን ነው? ስለረዳው፣ ስላጸደቀው፣ ስለሰማው፣ ስለሚረዳው ወ.ዘ.ተ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲሁ ስለ መውደዱ ግን አስቦ አያውቅም፡፡ የአንድ አማኝ ልዩ ፍላጎቱ ወደ መንግስተ ሰማያት መግባት ነው ወይ መንግስቱን የሚሰጠውን ጌታን መውረስ ነው? እኛና እግዚአብሔር ያለን ግንኙነት በጥቅማችን ላይ ብቻ ከተንጠለጠለ ፍቅራችን ጉዳዩ ላይ አንጂ ሰጪው ላይ አይደለም ማለት ነው፡፡ይሄ ደግሞ እንከን ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ኢየሱስን የሚወዱት የጸጋን ትምህርት ባልተስተካከለ ሁኔታ ሲሰሙ ነው

እንዲሁ መውደድ….. እንዴት የተወደዳችሁ ሆይ አንድ ሰው ጌታውን የሚወደው ለምንድን ነው? ስለረዳው፣ ስላጸደቀው፣ ስለሰማው፣ ስለሚረዳው ወ.ዘ.ተ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲሁ ስለ መውደዱ ግን አስቦ አያውቅም፡፡ የአንድ አማኝ ልዩ ፍላጎቱ ወደ መንግስተ ሰማያት መግባት ነው ወይ መንግስቱን የሚሰጠውን ጌታን መውረስ ነው? እኛና እግዚአብሔር ያለን ግንኙነት በጥቅማችን ላይ ብቻ ከተንጠለጠለ ፍቅራችን ጉዳዩ ላይ አንጂ ሰጪው ላይ አይደለም ማለት ነው፡፡ይሄ ደግሞ እንከን ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ኢየሱስን የሚወዱት የጸጋን ትምህርት ባልተስተካከለ ሁኔታ ሲሰሙ ነው፡፡ ለተወሰኑት ጸጋ በኃጢአት ለመኖር ከጌታ ኢየሱስ ፍቃድ የሚቀበሉበት ኪዳን ይመስላቸዋል፡፡ ያለ ኢየሱስ ለኔ ወገን የለኝም የሚሉ ጥቅሶችን፣ ነቆራ አዘል አባባሎችን መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ አይናቸውን ጨፍነው መዘመር ምናልባትም ከአይን ዘለላ እንባን ማውጣት ይጀምራሉ፡፡ በዚህ ወደ እግዚአብሔር እንደ ደረሱ ይሰማቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁል ጊዜ ከስንፍናቸው ጋር፣ ከድፍረታቸው ጋር፣ ከስድባቸው ጋር፣ ከፍርዳቸው ጋር፣ ከንቀታቸው ጋር፣ ከአሽሙራቸው ጋር አሉ፡፡ ጌታን የወደዱት ጸጋ ስላለ ነው እንጂ ሰውን መውደዱ፣ ንጽሕናው፣ ከልብ የዋህነቱ፣ ትህትናው፣ ለሰው ሟች መሆኑ ነክቷቸው አይደለም/ለአንዳንዶቹ/ ፡፡ ምክንያቱም ከጌታ ሕይወት የቅድስና ፍንጣሪ ነክቷቸው አይታይም፡፡ ለነሱ ግን ኢየሱስ ልዩ ነው ከአብም ከመንፈስ ቅዱስም ይበልጣል፡፡እነዚህ ሰዎች ጌታ ኢየሱስን የወደዱት በኃጢአት ከሚወቅሳቸው ህሊናቸው ወቀሳ በነጻ ጸድቃችኋል የተባለው ትምህርት ስላሳረፋቸው ብቻ ነው፡፡ ቅዱሳንን የምንወዳቸው ስለሚያማልዱን በረከታቸው ስለሚደርሰን ብቻ ነውን ? ይሄ ባይሆን ልንወዳቸው እንችላለን? አንዳንድ ሰዎች አከሌ አያማልድም የሚል ትምህርት ሲያሸንፋቸው ከልባቸው ስፍ ስፍ ብለው ይወዱት የነበረውን ቅዱስ ወደ መጥላት ይመጣሉ፡፡ በጆሯቸው ስለዛ ጻድቅ መስማት አይፈልጉም፡፡ ያው ወደዋለሁ አከብረዋለሁ ብለው ከልባቸው ጥላቻ ለመሸሽ በአፋቸው ብቻ ይሞክራሉ፡፡ ግን የእግዚአብሔርን እንቁዎች እንዲሁም ቢሆን ለምን መውደድ አቃታቸው? ቀሪዎቹ አከሌ እንዲህ አድርጎልኛልና እርሱ ለእኔ ይቅርታ አድርጉልኝ እንጂ ከእግዚአብሔር በላይ ሆኖ ይታየኛል ሲሉ ሳያፍሩ ይናገራሉ፡፡ ወንጌል ሰብኮ ለንስሃ ስላበቃቸው ክርስቶስን በኑሮው ማሳየቱ አይነካቸውም ዲቪ በስለት ስላገኙበት ነው የወደዱት፡፡ እነዚህ ሰዎች የሞተውን ቅዱስ እንጂ በሕይወት ያለውን ጻድቅ አይወዱም፡፡ እንደ ያዕቆብ ልጆች ቅዱሱን ይገድላሉ መቃብሩን ያሳምራሉ፡፡ ማቴ 23፤29-30 በሕይወት ቅዱስ የለም ብለው ያምናሉ፡፡ ጻድቅ ድሮ ቀረ ባዮች ናቸው፡፡ በሕይወት ዘመኑ ለእግዚአብሔር ሃሳብ ያደረውን ቅዱስ ከቤተክርስቲያን እስኪወገድ ድረስ ያሳድዱታል፡፡ እንደ ቀድሞዎቹ አይሁድ የክስ ዝርዝራቸው አያልቅም፡፡ ዛሬ ያለው የእግዚአብሔር ሰው አይረባም፡፡ እግዚአብሔርን ፈርተው እንጂ የዛሬው እግዚአብሔር ራሱ እንደ ድሮው አይደለም ለማለት ሁሉ ይፈልጋሉ፡፡ የዛሬው ቅዱስ ምዕመን፣ ጳጳስ፣ ሰባኪ፣ ዘማሪ፣ አስተናባሪ ፣ መካሪ፣ ሰንበት ተማሪ ምንም ረብ የሌለው ተራ ነው፡፡ የሞቱት ግን ስለሚጠቅሟቸው የከበሩ ናቸው፡፡ ባይጠቅሟቸው ግን እነርሱንም አይጠቅሙም ባይ ይሆኑ ነበር፡፡ስለዚህ በስሙ የምታመኑ ሆይ ከጌታችን ከመድሃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከከበረው መምህር አባት እንዲሁ መውደድን ልንማር ይገባል፡፡ አንድ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን አንዲሁ ወዷል፡፡ዮሐ3፤16 ተብሎ ተጽፏል፡፡ እግዚአብሔርም ስለጠቀመን ብቻ ሲወደድ ደስ የሚለው አይመስለኝም፡፡ ጻድቁም ስለጠቀመ ብቻ ከተከበረ ደስ የሚለው አይደለም፡፡ ጥቅሙ በረከቱ ዳረጎት ሆኖ ይሰጣል፡፡ በእምነት የሆነ ፍቅር በነጻ የሆነ መውደድ እጅግ ደስ ያሰኛል፡፡ያለ እምነት የሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው፡፡ሮሜ 14፤23 እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment