Friday, September 19, 2014

ሰላም ለሁላችሁ፤- ምህረቱ ለሚፈሩት እስከ ትውልድ ትውልድ ነው…ሉቃ 1፤50 በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ሆይ፤- እግዚአብሔርን በፍቅር መፍራት ስለእርሱ ከማወቅ ይጀምራል፡፡ ጌታችሁን የምታውቁት ስለርሱ ፍላጎትና ፍለጋ ሲኖራችሁ ነው፡፡ በርግጥ አሁን ያላችሁበት ኑሮ የማንንም እርዳታ የማይፈልግ ይሆናል፡፡ ጊዜአችሁን ምቾታችሁን ሊያስጠብቅላችሁ ይችላል በምትሉት ነገር ብታጠፉ ደስ ይላችኋል፡፡ ነገር ግን እናንተ የዛሬው ሰዎች ብቻ አይደላችሁም የምድርም ኑሮ ብቻ አይደለም ያላችሁ፡፡ትውልዳችሁን የሚረከብ ጌታ አለ፡፡ ዘላለም የሚባል ዓለም አለ፡፡ ወደዛ የምትደርሱበት መንገድ ጌታ ነው ፡፡ ለትውልዳችሁ የምታወርሱት ከምድር የሆነ ጌጠኛ ድንጋይ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ እንደ አብርሃም የዘላለም ምህረት የመለኮት ጥበቃ ለልጆቻችሁ ማቆየት አለባችሁ፡፡ ይህን የምታገኙት ልዑሉን ስታውቁትና ስትፈሩት ነው፡፡ ለትውልዳቸው ርግማን ትተው ያለፉ የትናንት ሰዎች ነበሩ፡፡ የሰው ደም በከንቱ ያፈሰሱ፣ በድሃ እንባ የታጠቡ፣ ሃገር ያፈረሱ፣ ልዑሉን የረገሙ፣ ማምለኪያውን ያቃጠሉ፣ በጉቦ የፈረዱ፣ ባይተዋሩን ፊት የነሱ… እነዚህ መርገምን ለትውልዳቸው ትተው ሄደዋል፡፡ የፈሩት ግን ተመርቀዋል ከነልጆቻቸው ምህረትን ጠግበዋል፡፡የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ምሳ 1፤7 ተባረኩ፡፡ እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት visit www.ashenafigmariam.blogspot.com

No comments:

Post a Comment