Wednesday, September 24, 2014

ሰላም ለሁላችሁ፤- መስቀል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማንን ተሸክሞ በእንጨት መስቀል መሰቀሉን የምናስብበት ነው

ሰላም ለሁላችሁ፤- መስቀል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማንን ተሸክሞ በእንጨት መስቀል መሰቀሉን የምናስብበት ነው፡፡ ገላ 3፤13 መሰቀሉ የጌታን አሸናፊነት ያሳየ ነው፡፡ ክርስቶስ ገዳዮችን ብቻ ሳይሆን ሞትን የተዋጋ ነጻ አውጪ ነው፡፡ በመስቀል ሲሞትም እየማረከ ከፍ እያለ ነበር እንጂ እንደ ሰው እያለቀለት አልነበረም፡፡ ምክንያቱም ትግሉን በትንሳኤ ደምድሞታል፡፡ ስለዚህ ሞቱን ክብር ብሎ ጠርቶታል፡፡ ዮሐ 17፤2 መሰቀሉም ወደ ላይ ከፍ ማለቱ ነበር፡፡ ተሰቀለ ከፍ ከፍ አለ ማለት ነው፡፡..እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደሆነ ሁሉን ወደ እኔ እሰበስባለሁ..ዮሐ 12፤32 እንዳለ፡፡ እኛም በመሰቀሉ ወደ ላይ ክፍ ብለናል፡፡ ወደ ፊት ወደ እርሱ ለመነጠቅ ከበጉ ሰርግ ለመታደም በተስፋ የምንጠብቅበትን መግባት አግኝተናል፡፡ ምልክቱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነው … ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሳታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ሆኖ ተሹሟል…ሉቃ 2፤35 መስቀሉም በጉ የተሰዋበት ቅዱስ መሰዊያ ነው፡፡ ያዳኛችንን ቅዱስ ሞት የምናስብበት ነው፡፡ መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ፡፡ እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት www.ashenafigmariam.blogspot.com

No comments:

Post a Comment