Monday, September 23, 2013

ሰላም ለሁላችሁ፤- እንዲህ ያለው ግብዝነት የሌለበት እምነት በአያትህ በሎይድ በእናትህ በኤውንቄ ነበረባቸው 2ኛ ጢሞ 1;5 ግብዝነት ያለበት እምነት የሚሰራው በሰው ፊት ነው፡፡ ማመኑ ለሰዎች ጥቅም ከመሆን ይልቅ የሰውን ህሊና ማናደጃ፣ የተደበቀ አለማዊነት በውስጡ የሚሰራ ነው፡፡



ሰላም ለሁላችሁ፤- እንዲህ ያለው ግብዝነት የሌለበት እምነት በአያትህ በሎይድ በእናትህ በኤውንቄ ነበረባቸው 2ኛ ጢሞ 1;5   ግብዝነት ያለበት እምነት የሚሰራው በሰው ፊት ነው፡፡ ማመኑ ለሰዎች ጥቅም ከመሆን ይልቅ የሰውን ህሊና ማናደጃ፣ የተደበቀ አለማዊነት በውስጡ የሚሰራ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ በዘመናችን እኔ የማርያም ነኝ ወይ እኔ የኢየሱስ ነኝ የሚሉ ፉከራዎችን የምናገኘው ግብዝነት ጓዙን ጠቅልሎ ስለገባብን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እኔ የአጵሎስ ነኝ እኔ ኬፋ እኔ የጳውሎስ እኔ የክርስቶስ ነኝ ያሉ ግብዞችን ከዚህ ስንፍናቸው እንዲላቀቁ መከረ፡፡1ኛ ቆሮ 1፤12  የክርስቶስ፣ የጳውሎስ፣ የኬፋ፣ የአጵሎስ፣ የማርያም ድንግል መሆን ባልከፋ እምነቱ ግን በእግዚአብሔር ፊት ባለዋጋ ከመሆን ይልቅ ግልጽ ድንጋዩን ጥለን ያነሳነው ሌላ መንፈሳዊ ጦር መሳርያ/ስውር ድንጋይ/ ሆኖ እምነት መልኩን እንዲያጣ ጣዕሙን እንዲቀይር የመንፈሳዊነት መዓዛ እንዲጠፋ አድርጓል፡፡ አንዳንድ አማኖች የእግዚአብሔር ሰው ከመሆን ይልቅ ኦርቶዶክሶች ናቸው እንዲባሉ ላይ ላዩን ለመምሰል ይሞክራሉ፡፡አኒህ ሰዎች ጾማቸውን በሰው ፊት ያደረጉትን የዋሆች ይመስላሉ፡፡ደግሞ ሌሎቹ የኢየሱስ ተቆርቋሪ ሆነው በክፉ ትዕቢታቸው ኢየሱስን የሚያጠቁሩ አሉ፡፡እነሎይድ ግን ግብዝነት በሌለበት እምነት ተመሰገኑ እምነታቸው አይመካም እዩኝ እዩኝ አይልም እንደነኤልሳቤጥ በእግዚአብሔር ፊት የሆነ እና በመንፈስ ቅዱስ የተመሰከረለት ነው፡፡ሉቃ 1;6
እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment