Monday, March 31, 2014

ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡-

ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡- እናት አባት ሳይኖራችሁ ሰው ከወላጅ ሊቀበለው የሚገባውን ፍቅር ተርባችሁ ስታድጉ ወላጅ ሆኖ እየሞላ ሳያጎድል ያሳደጋችሁ እግዚአብሔር አይደለም? እስቲ ተናገሩ፤- መልካም ያላችሁት ሰው ባስቀመጣችሁት ቦታ ሳይገኝ፣ ሚስጢራችሁን አውቆ ሲሳለቅባችሁ ልባችሁ ተሰብሮ ሳለ መንፈስ ቅዱስ ደርሶ ትናትን አላስረሳችሁም? ኑሮዬን ከርሱ/ሷ ጋር አድረጋለሁ ብላችሁ ብዙ ዋጋ የከፈላችሁበት ትዳርና ጓደኝነት ገደል ገብቶ በራችሁን ዘግታችሁ ስታለቅሱ መጥቶ እንባችሁን ያበሰ ጌታ አልነበረም? እስቲ ተናገሩ፤- ሞት ከደጃችሁ የቀረበ እስኪመስላችሁ በብርቱ ታማችሁ በራሳችሁ ተስፋ ቆርጣችሁ ሳለ ቆማችሁ እንድትሔዱ የሆናችሁት በአምላካችሁ እጅ አይደለምን? ውስጣችሁ ከተቀበረ አሳዛኝ ታሪካችሁ ጋር የተቀበላችሁ ጌታ ኢየሱስ አይደለምን?ማቴ 11፤28 ተለወጠ ስትሉት ሳይለወጥ ተወኝ ስትሉት ሳይተው ተቆጣ ስሉት ወዶ… ያሳደራችሁ መልካም አሳዳሪ ጌታችሁ አይደለምን ?እስቲ ተናገሩ፡- በእዳ ተይዛችሁ እዳችሁን የከፈላችሁበት፣ ተገፍታችሁ የፈረደላችሁ፣ ዲዳ ናቸው ብለው ሲከሷችሁ የተናገረላችሁ፣ እንዴት እኖራለሁ ብላችሁ ያኖራችሁ እንዴት እለምዳለሁ ብላችሁ ሃገር ያስለመዳችሁ እንደጥላ የሚከተላችሁ እግዚአብሔር አይደለምን…….pls share it ብቸኝነቴን ያስረሳኝ ወላጅ ደጋፊ የሆነኝ ሰላላ ክንዴን ያበረታ እርሱ ብቻ ነው የኔ ጌታ ይፍሰስ እንባዬ ይሙላኝ አንክሮ ፍቅሩ ሲነካኝ ዓለቴን ሰብሮ አለ በልቤ የእርሱ መብራት መልካምነቱን የማይበት ዘማሪ ዳዊት በቀለ ቁ 2 /በቅርብ የሚወጣ ዝማሬ/

No comments:

Post a Comment