Monday, March 31, 2014
ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡-
ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡- እናት አባት ሳይኖራችሁ ሰው ከወላጅ ሊቀበለው የሚገባውን ፍቅር ተርባችሁ ስታድጉ ወላጅ ሆኖ እየሞላ ሳያጎድል ያሳደጋችሁ እግዚአብሔር አይደለም? እስቲ ተናገሩ፤- መልካም ያላችሁት ሰው ባስቀመጣችሁት ቦታ ሳይገኝ፣ ሚስጢራችሁን አውቆ ሲሳለቅባችሁ ልባችሁ ተሰብሮ ሳለ መንፈስ ቅዱስ ደርሶ ትናትን አላስረሳችሁም? ኑሮዬን ከርሱ/ሷ ጋር አድረጋለሁ ብላችሁ ብዙ ዋጋ የከፈላችሁበት ትዳርና ጓደኝነት ገደል ገብቶ በራችሁን ዘግታችሁ ስታለቅሱ መጥቶ እንባችሁን ያበሰ ጌታ አልነበረም? እስቲ ተናገሩ፤- ሞት ከደጃችሁ የቀረበ እስኪመስላችሁ በብርቱ ታማችሁ በራሳችሁ ተስፋ ቆርጣችሁ ሳለ ቆማችሁ እንድትሔዱ የሆናችሁት በአምላካችሁ እጅ አይደለምን? ውስጣችሁ ከተቀበረ አሳዛኝ ታሪካችሁ ጋር የተቀበላችሁ ጌታ ኢየሱስ አይደለምን?ማቴ 11፤28 ተለወጠ ስትሉት ሳይለወጥ ተወኝ ስትሉት ሳይተው ተቆጣ ስሉት ወዶ… ያሳደራችሁ መልካም አሳዳሪ ጌታችሁ አይደለምን ?እስቲ ተናገሩ፡- በእዳ ተይዛችሁ እዳችሁን የከፈላችሁበት፣ ተገፍታችሁ የፈረደላችሁ፣ ዲዳ ናቸው ብለው ሲከሷችሁ የተናገረላችሁ፣ እንዴት እኖራለሁ ብላችሁ ያኖራችሁ እንዴት እለምዳለሁ ብላችሁ ሃገር ያስለመዳችሁ እንደጥላ የሚከተላችሁ እግዚአብሔር አይደለምን…….pls share it
ብቸኝነቴን ያስረሳኝ
ወላጅ ደጋፊ የሆነኝ
ሰላላ ክንዴን ያበረታ
እርሱ ብቻ ነው የኔ ጌታ
ይፍሰስ እንባዬ ይሙላኝ አንክሮ
ፍቅሩ ሲነካኝ ዓለቴን ሰብሮ
አለ በልቤ የእርሱ መብራት
መልካምነቱን የማይበት ዘማሪ ዳዊት በቀለ ቁ 2 /በቅርብ የሚወጣ ዝማሬ/
Labels:
መጽናኛ
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment