Monday, October 21, 2013

ሰላም ለሁላችሁ፤- አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው፡፡ ያዕ 1፤26 አንደበት የሰማይንም የምድርንም ፍጥረታት የሚያስቆጣ ክፉ ነገር የሚወጣት በር ነው፡



ሰላም ለሁላችሁ፤- አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው፡፡ ያዕ 1፤26 አንደበት የሰማይንም የምድርንም ፍጥረታት የሚያስቆጣ ክፉ ነገር የሚወጣት በር ነው፡፡ ነገር ግን መዝጊያ ተበጅቶለታል፡፡ ያም እግዚአብሔርን የሚፈራ አእምሮ ነው፡፡ ደግሞም እሳት የሚተፋ እስካሁን ዘመን ድረስ ሳይጠፋ ያለ ደራጎን ነው፡፡ ዓለምን ማቃጠል የሚችል እሳት ይወጣበታል፡፡ እንዲሁም መልካም ህሊና ላለውም ሰው የሞቱ ልቦች የሚነቃቁበት መንፈሳዊ ሙቀት የሚወጣበት ቅዱስ እሳት መፍሰሻ ነው፡፡ በጌታም ዘንድ የምንዳኝበት  መረጃ ነው፡፡ በፍርድ ቀን ለምንናገረው ለእያንዳንዱ ነገር መልስ  ትሰጣላችሁ ብሎናል ጌታችነ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ ስለዚህ እንደፈለገ የሚንሸራተት አንደበታችንን ዝም አንበለው፡፡ ለጌታ ክብር ፣ ለሃይማኖት ወ.ዘ.ተ.   ብለህ ነውና አንደበትህ ቢረክስ ችግር የለውም የሚለንን የዲያቢሎስን ማባበል በስሙ ልንገስጸው ይገባል፡፡የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሰራም ተብሎ ተጽፏልና፡፡ያዕ 1፤20
እባካችሁ ለሌሎች ሼር አድርጉት

No comments:

Post a Comment