Showing posts with label መጽናኛ. Show all posts
Showing posts with label መጽናኛ. Show all posts

Monday, March 31, 2014

ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡-

ሰላም ለሁላችሁ፤- እስቲ ተናገሩ፡- እናት አባት ሳይኖራችሁ ሰው ከወላጅ ሊቀበለው የሚገባውን ፍቅር ተርባችሁ ስታድጉ ወላጅ ሆኖ እየሞላ ሳያጎድል ያሳደጋችሁ እግዚአብሔር አይደለም? እስቲ ተናገሩ፤- መልካም ያላችሁት ሰው ባስቀመጣችሁት ቦታ ሳይገኝ፣ ሚስጢራችሁን አውቆ ሲሳለቅባችሁ ልባችሁ ተሰብሮ ሳለ መንፈስ ቅዱስ ደርሶ ትናትን አላስረሳችሁም? ኑሮዬን ከርሱ/ሷ ጋር አድረጋለሁ ብላችሁ ብዙ ዋጋ የከፈላችሁበት ትዳርና ጓደኝነት ገደል ገብቶ በራችሁን ዘግታችሁ ስታለቅሱ መጥቶ እንባችሁን ያበሰ ጌታ አልነበረም? እስቲ ተናገሩ፤- ሞት ከደጃችሁ የቀረበ እስኪመስላችሁ በብርቱ ታማችሁ በራሳችሁ ተስፋ ቆርጣችሁ ሳለ ቆማችሁ እንድትሔዱ የሆናችሁት በአምላካችሁ እጅ አይደለምን? ውስጣችሁ ከተቀበረ አሳዛኝ ታሪካችሁ ጋር የተቀበላችሁ ጌታ ኢየሱስ አይደለምን?ማቴ 11፤28 ተለወጠ ስትሉት ሳይለወጥ ተወኝ ስትሉት ሳይተው ተቆጣ ስሉት ወዶ… ያሳደራችሁ መልካም አሳዳሪ ጌታችሁ አይደለምን ?እስቲ ተናገሩ፡- በእዳ ተይዛችሁ እዳችሁን የከፈላችሁበት፣ ተገፍታችሁ የፈረደላችሁ፣ ዲዳ ናቸው ብለው ሲከሷችሁ የተናገረላችሁ፣ እንዴት እኖራለሁ ብላችሁ ያኖራችሁ እንዴት እለምዳለሁ ብላችሁ ሃገር ያስለመዳችሁ እንደጥላ የሚከተላችሁ እግዚአብሔር አይደለምን…….pls share it ብቸኝነቴን ያስረሳኝ ወላጅ ደጋፊ የሆነኝ ሰላላ ክንዴን ያበረታ እርሱ ብቻ ነው የኔ ጌታ ይፍሰስ እንባዬ ይሙላኝ አንክሮ ፍቅሩ ሲነካኝ ዓለቴን ሰብሮ አለ በልቤ የእርሱ መብራት መልካምነቱን የማይበት ዘማሪ ዳዊት በቀለ ቁ 2 /በቅርብ የሚወጣ ዝማሬ/

Wednesday, July 10, 2013

ሰላም ለሁላችሁ

ሰላም ለሁላችሁ፤- እግዚአብሔር ሰውን የሚረዳው ወይም/underesatand/ የሚያደርገው በምን መጠን እንደሆነ አስባችሁ ታውቃላችሁ? ሰው ለእግዚአብሔር ችግሩን ድካሙን ሲነግረው እርሱ የሚሰማው ከጀርባው ታሪኩ ተነስቶ ነው ከአስተዳደጉ፣ ከደረሰበት ማህበራዊ ተጽዕኖ፣ ከስነልቦና ችግሩ፣ ወንጌልን ካለመማሩ፣ የሰው እርዳታ ካለማግኘቱ፣ የተጎዳ ከመሆኑ ከእነዚህ ሁሉ ችግሮቹ ተነስቶ ይሰማዋል፡፡ ስለዚህም ጨክኖ አይፈርድበትም ይራራለታል እንጂ! አብዛኛው ሰው ብዙውን ጊዜ አንድን ሰው የሚዳኘው ስለሰውየው በሰማው ወይ አልፎ አልፎ ባየው ነገር ይሆንና ሳይራራ ይወስንበታል፡፡ መጥላት ካለበትም ከዚያ ቀን ጀምሮ ይጠላዋል ይሸሸዋል፡፡ ጌታ የተለየ ነው፡፡ ባለችግሩን ከችግሩ ሳያወጣ አይተወውም፡፡ ሰባራውን ጠጋኝ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ እመኑኝ እግዚአብሔር ስለእግዚአብሔር እንደሰማነው አይደለም፡፡ እኛ እንኳ ሰው ስለእኛ እንደሚናገረው አይደለንም እኮ! አምላካችን ግን ምን ያህል መሃሪ፣ ምን ያህል ታጋሽ፣ ምን ያህል ረዳት፣ ምን ያህል ተሸካሚ ምን ያህል አስፈሪ፣ ምን ያህል ታላቅ፣ ምን ያህል ቅን ደግሞም ምን ያህል አስፈሪ እንደሆነ ማን ሊገምት ይችላል? እባካችሁ እግዚአብሔር ይቀፋችሁ አምላካችሁ ያኑራችሁ ጌታችሁ እንደገና ይስራችሁ፤